የስደተኝነት ማመልከቻ ብቁነት ላይ ተፅእኖ የሚኖራቸው ኣዲስ ህጎች
ከ መጋቢት 26-2026 ጅምሮ ቢል ሲ -12 ( Bill C-12 ) የተባለ የስደተኝነት ጥያቄ ማመልከቻን የሚመለከት ህግ ተግባራዊ ሆናል ።
ኣዲስ የብቁነት ህጎች
እነዚህ ኣዲስ ህጎች ከ ስኔ 3-2025 ጀምሮ በገቡት ሁሉም ማመልክቻዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ።
ከሚከተሉት ውስጥ ከሆነ ማመልከቻዎ ወደ ኢሚግረሽን እና ስደተኞች ቦርድ ( IRB ) ለመላክ ብቁ ኣይሆንም ።
- * ወደ ካናዳ ለመጀመርያ ግዜ ገብተው የስደተኛ ማመልከቻዎን ሳያስገቡ ከኣንድ እመት በላይ ከቆዩ ( ከ ሰኔ 24-2020 ቦሃላ ) ከኣገሪትዎ ወጥተው ተመልሰው የገቡም ቢሆን ።
- * ወደ ካናዳ ብይፋዊ መተላለፍያ ድንበሮች ገብተው የስደተኝነት ማመልከቻዎን ከገቡበት ቀን ጀምሮ ከ 14 ቀናት በላይ ቆይተው ካቀረቡ*
* የሶስተኛ ደህንነታቸው የተጠበቁ ኣገሮች ስምምነት (STCA) ኣሁንም ስራ ላይ እንደዋለ ነው ። ወደ ካናዳ ብይፋዊ መተላለፍያ ድንበሮች ገብተው በ 14 ቀናት ውስጥ ማመልከቻዎን ኒያስገቡም ፣ ማመልከቻዎ ወደ IRB ለመላክ ብቁ ሆኖ ኣይገኝም ፣ በ STCA ጉዳይዎ በልዩ ሁኔታ እንዲታይ ከተፈቀድልዎ በስተቀር ።
ለተጨማሪ ዘርዘር ያለ የ ብቁነት መረጃ ፣ የ IRCC ድህረ ገፅን ይመልከቱ :
- በድንበር የመግባት ማመልከቻ ( ኣየር ማረፍያ ወይም ይፋዊ የድንበር ማቃረጫ )Port of Entry claim
- ባገር ውስጥ ማመልከቻ ( ካናዳ ውስጥ የሆነ ) Inland claim
ኣስፈላጊ : IRCC እና CBSA ከ ስኔ 3-2025 ቦሃላ የቀረቡትን ሁሉን ማመልከቻዎች ደግመው እየመረመሩ ነው ። ማመልከቻዎ በዚህ ኣዲስ ህግ የሚመለከተው ከሆነ ፣ እርስዎን እና ህጋዊ ወኪልዎን እናነጋግራለን ። IRB ፣ IRCC ፣ CBSA፣ እና ህጋዊ ወኪልዎ እርስዎ ወቅታዊ የሚገኙበትን መረጃ እንዳላቸው ያረጋግጡ ።
ማመልከቻዎ ወደ IRB ለመቅረብ ብቁ ካልሆነ
የስደተኝነት ማመልከቻዎ ብቁ ካልሆነ ፣ ወደ ካናዳ የድንበር ኣገልግሎት ኤጀንሲ ( CBSA ) ይላካሉ ። CBSA ደግሞ ለቅድመ መንቀሳቀስ ሪስክ ግምገማ ( PRRA) ማመልከት ይችሉ እንደሆነ ይወስናል ።
PRRA ማለት ወደ መጡበት ኣገር ተመልሰው ከተላኩ የደህንነት ስጋት ፣ ስቃይ እና መጥፎ ኣያያዝ ያጋጥመኛል ካሉ ያንን ለመከላከል የሚደረግ ማማመልከቻ ነው ። PRRA እንደ የስደተኛት የመሰማት ችሎት ኣይደለም ።ነገር ግን ተቀባይነት ካገኙ ጥገኝትን ሊያገኙ ይችላሉ ።
ድጋፍ እና መረጃ ማግኘት
- ስለስደተኝነት ማመልከቻዎ ብቁነት ወይንም ያሳሰብዎት ጥያቄዎች ካለዎት መረጃን ያግኙ ወይንም ከጠበቃዎ ወይም የህግ ተወካይዎ ምክር ያግኙ
- ።የመልሶ ማቃቃም ድርጅቶች እነዚህን ኣዳዲስ ህጎች ለመረዳት እና ከህግ ተወካዬችዎ/ ጠቃሚ ነገሮች ጋር እንዲገናኙ ይረዳሉ
የነዛን ተቃማትን ዝርዝር ለማግኘት ፣ ይሄንን ይመልከቱ Community Resources
