የ ስደተኝነት ማመልከቻዎን ቀድመው ያስገቡ ቢሆንም እንካን በካናዳ የወጡ ኣዲስ ህጎች የስደተኝነት ማመልከቻዎ ላይ ተፅእኖ ሊኖራቸው ይችላል ። እዚህ ዌብሳይት ላይ የሚገኙ ኣንዳንድ መረጃዎች ቀናቸው ያለፈባቸው ናቸው ። ወቅታዊ እያደረግናቸው እንገኛለን ። ጠበቃዎን ወይንም የሚታመንን የመልሶ ማቃቃም ኣገልግሎት ኣቅራቢን ያነጋግሩ ። ለተጨማሪ መረጃ

በእስር ላይ

ሰዎችን ማነጋገር

ከኢሚግሬሽን መያዣ ማዕከል ወይም እስር ቤት ውጭ ካሉ ሰዎች ጋር መነጋገር ከባድ ሊሆን ይችላል።

በኢሚግሬሽን መያዣ ማእከላት ኢንተርኔትን ወይም የራስዎን ሞባይል ካናዳ ድንበር አገልግሎት ኤጀንሲ (CBSA) ካልፈቀዱ በስተቀር መጠቀም አይችሉም። በካናዳ ውስጥ ነፃ ጥሪ ማድረግ ይችላሉ። ወደ ሌላ ሀገር ለመደወል የቅድመ ክፍያ ዓለም አቀፍ የጥሪ ካርድ ሊያስፈልግዎ ይችላል።

እስር ቤት ውስጥ፣ በየትኛው ውስጥ እንዳሉ ተመስርቶ ስልክ መጠቀም ላይ ችግር ሊኖርብዎት ይችላል።

መረጃ ያግኙ

ስለሚቀጥሉት እርምጃዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የካናዳ ድንበር አገልግሎት ኤጀንሲ (CBSA) መኮንንን ለማነጋገር መጠየቅ ይችላሉ። የእርስዎ ህጋዊ ተወካይ ጠቃሚ መረጃም ሊሰጥዎት ይችላል።

አሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (NGO) የታሰሩ ሰዎችን የሚደግፉ።እነሱ ሊጎበኙዎት እና ስለሁኔታዎ መረጃ ሊሰጡዎት ይችላሉ። መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ( NGO) ማነጋገር ከቻሉ የካናዳ ድንበር አገልግሎት ኤጀንሲ (CBSA) መኮንንን ወይም የህግ ተወካይዎን ይጠይቁ።

ጎብኝዎች

ከጓደኞቾ፣ የቤተሰብ አባላት ወይም ሌሎች ጉብኝቶች ሊኖሩዎት ይችላሉ። የጉብኝት ሰዓቶች እና ሁኔታዎች ይለያያሉ።

የደህንነት እርምጃዎች

የማያዣ ማእከሎች እና እስር ቤቶች ህጎቹን በሚያስከብሩ እና እርስዎን በሚጠብቁ በጠባቂዎች የተያዙ ናቸው።

መታሰር በጣም ከባድ ተሞክሮ ሊሆን ይችላል። እስር ቤት ይመስላል እና መሰረታዊ ነጻነቶች አይኖሩዎትም። ከተቋሙ ውጭ በሚሆኑበት ጊዜ (ለምሳሌ ለውጭ የህክምና ቀጠሮዎች) የእጅ ማሰሪያ፣ ሰንሰለት እና ሌሎች ማገጃዎች ጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ።

ልጆች

ከልጆችዎ ጋር ካናዳ ውስጥ ከሆኑ፣ ከእርስዎ ጋር በአንድ ማእከል ውስጥ ሊያዙ ይችላሉ። ከልጆችዎ ወይም ከሌሎች የቤተሰብ አባላት ከተለዩ ለህጋዊ ተወካይዎ ይንገሩ እና ከመንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ( NGO ) እርዳታ ያግኙ።

ቅሬታ አቅርቡ

ስለ ህክምናዎ ቅሬታ ካለዎት፣ ለካናዳ ድንበር አገልግሎት ኤጀንሲ (CBSA) ቅሬታ ማቅረብ ይችላሉ። ያደረጓቸው ማናቸውም ውይይቶች በችሎትዎ ላይ እንደገና ሊመጡ ይችላሉ። የሕግ ምክር ማግኘት ወይም ከመንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት(NGO) መረጃ ማግኘት አስፈላጊ ነው።

መብቶችዎ

በእስር ላይ እያሉ፣ የሚከተሉትን ለማድረግ መብት አልዎት፡-

  • ለምን እንደታሰሩ የመነገር መብት አልዎት።
  • የ ካናዳ ድንበር አገልግሎት ኤጀንሲ (CBSA) መኮንን ማግኘት መብት።
  • እንግሊዘኛ ወይም ፈረንሳይኛ የማይረዱ ወይም የማይናገሩ ከሆነ አስተርጓሚ የማግኘት መብት።
  • ህክምና የማግኘት መብት ።
  • የሃይማኖት ተግባራት የመፈፀም መብት።
  • ለእርስዎ የሚሰራ የህግ ተወካይ የመቅጠር መብት።
  • ብቁ ከሆኑ የህግ እርዳታ ያግኙ። ስላለዎት የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ይነገርዎታል። እንዲሁም ጓደኛ ወይም የአንድ ድርጅት አባል እንዲወክልዎት ያለክፍያ ማግኘት ይችላሉ።
  • የአገርዎን ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ያነጋግሩ። የስደተኛ ጥያቄ እያቀረቡ ከሆነ በመጀመሪያ የህግ ምክር ሳያገኙ ይህን ማድረግ የለብዎትም። በካናዳ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) እንዲገናኝ መጠየቅ ይችላሉ።
  • እርስዎን ሊደግፉ የሚችሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን (NGO) ያነጋግሩ።