የካናዳ የኢሚግሬሽን እና የስደተኞች ቦርድ – የስደተኞች ጥበቃ ክፍል (IRB-RPD) የስደተኛ ጥያቄዎ በካናዳ ተቀባይነት ይኖረው እንደሆነ ይወስናል።
በስደተኛ ችሎትዎ መጨረሻ ላይ የቦርዱ አባል የሚከተሉትን ማድረግ ይችላል፡-
- ችሎቱ በቀጣይ እንዲቀጥል የሚያስፈልግ ከሆነ ይንገርዎታል።
- የይገባኛል ጥያቄዎ ተቀባይነት ካገኘ ወይም ውድቅ ከተደረገ ይነግርዎታል። ይህ የቃል ውሳኔ ይባላል።
- ከመሰማት ችሎቱ ቦሃላ ውሳኔውን የህግ ተወካይዎ ይላካል ። ይህ የጽሁፍ ውሳኔ ይባላል።
- እርስዎ ወይም የህግ ተወካይዎ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት ተጨማሪ ሰነዶችን ወይም መረጃዎችን ለመላክ በቂ ጊዜ ይስጣቿል።
